ሀብታሙ ግርማ
የካቲት 13 ቀን 2012 ዓ.ም
ጅግጅጋ፣ኢትዮጵያ


የኢትዮጵያ ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ ባወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ፓርቲዎች የምረጡኝ ቅስቀሳ የሚጀምሩበት ወቅት ባለፈው ሳምንት ይፋ ሆኗል። አሁን ባለው የአገራችን ነባራዊ ሁኔታ ጠብ እንደማንሳት ቀላል ነገር የለምና የምረጡኝ ቅስቀሳው ወቅት ደንበኛ የጠብ ወቅት ሊሆን የሚችልበት እድሉ ሰፊ ነው።

ነገሩን አሳሳቢ የሚያደርገው ደግሞ ማህበረሰባችን የአመራር ቀውስ በገጠመው በዚህ ወቅት የምርጫ ቅስቀሳ ሊከወን መሆኑ ነው። ዛሬ በኢትዮጵያ ጠብን የሚያሟሙቅ እንጂ የሚያበርድ መሪ ወይም አስታራቂ ሽማግሌ ማግኘት ከባድ ነውና መራጩ ህዝብ የጠብ መንገዶችን መዝጋት ይገባዋል። ይህም ሲባል የምርጫ ቅስቀሳ መድረኮችን ከመደገፍ አንጻር እንጂ ከመቃወም አንጻር ማየት የለበትም ለማለት ነው።

ለምሳሌ ኢዜማ በሚጠራው የድጋፍ ሰልፍ ላይ የአብን ወይም የኦነግ ደጋፊ በሰልፉ መገኘቱ ለምን ይሆናል?
ኦነግ በሚጠራው የአደባባይ ምረጡኝ ቅስቀሳ የብልጽግና ፖርቲ ደጋፊ ምን ይሰራል?

ስለዚህ ለሚቀጥሉት አራት ወራት የወጣው ምርጫ የጊዜ ሰሌዳ ለስድብ ወይም ቧልት፣ ከፍ ሲልም ለብሽሽቅ እና ጠብ አጫሪነት ሳይሆን ለስልጡን ዲሞክራሲያዊነት መጠቀም ያሻል። የምረጡኝ ዘመቻ ወቅቱን የምንደግፈውን ፓርቲ ፕሮግራሞችን ለመገምገም እንጂ ለብሽሽቅ መጠቀም የለብንም።


Discover more from Habtamu Girma Demiessie (ሀብታሙ ግርማ ደምሴ)

Subscribe to get the latest posts to your email.

Published by Habtamu Girma Demiessie (ሀብታሙ ግርማ ደምሴ)

Habtamu Girma Demiessie is assistant professor of Economics at Jigjiga University, Ethiopia. An academic and a writer, Mr. Habtamu authored 8 books and published more than 85 scholarly works. His academic & literary works, which can be categorized as original research article, commentary, opinion or view point pieces, appeared on well read journals, Newsletters, print media and/or social media outlets in Ethiopia and abroad Readers interested to throw comments and/or critics on his works may contact the author via the following addresses: E-mail: • ruhe215@gmail.com • hab200517@yahoo.com Telephone (Mob): • +251 (0) 912 064 095. Website/Blog sites: •https://www.jigjigauniversity.academia.edu/HabtamuGirma •https://www.ruhehabtamu.wordpress.com/HabtamuGirma •https://www.researchgate.net/profile/Habtamu_Demiessie2

አስተያየት ያስቀምጡ

ይህ ጣቢያ አይፈለጌ መልዕክትን ለመቀነስ Akismet ይጠቀማል። የአስተያየትዎ ውሂብ እንዴት እንደሚሰናዳ ይወቁ

Discover more from Habtamu Girma Demiessie (ሀብታሙ ግርማ ደምሴ)

Subscribe now to keep reading and get access to the full archive.

Continue reading

Design a site like this with WordPress.com
ጀምር