የምርጫ ቅስቀሳው ወደ ጸብ ቅስቀሳ እንዳይቀየር እንጠንቀቅ!

የኢትዮጵያ ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ ባወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ፓርቲዎች የምረጡኝ ቅስቀሳ የሚጀምሩበት ወቅት ባለፈው ሳምንት ይፋ ሆኗል። አሁን ባለው የአገራችን ነባራዊ ሁኔታ ጠብ እንደማንሳት ቀላል ነገር የለምና የምረጡኝ ቅስቀሳው ወቅት ደንበኛ የጠብ ወቅት ሊሆን የሚችልበት እድሉ ሰፊ ነው።

ነገሩን አሳሳቢ የሚያደርገው ደግሞ ማህበረሰባችን የአመራር ቀውስ በገጠመው በዚህ ወቅት የምርጫ ቅስቀሳ ሊከወን መሆኑ ነው። ዛሬ በኢትዮጵያ ጠብን የሚያሟሙቅ እንጂ የሚያበርድ መሪ ወይም አስታራቂ ሽማግሌ ማግኘት ከባድ ነውና መራጩ ህዝብ የጠብ መንገዶችን መዝጋት ይገባዋል። ይህም ሲባል የምርጫ ቅስቀሳ መድረኮችን ከመደገፍ አንጻር እንጂ ከመቃወም አንጻር ማየት የለበትም ለማለት ነው።

Design a site like this with WordPress.com
ጀምር